input
stringlengths 1
130k
⌀ |
---|
በ እና ዓም በብዙ አፍሪቃውያት ሀገራት ውስጥ ተቃውሞ ተካሂዷል።
|
በዚምባብዌ እና በዴሞክራቲክ ኮንጎ ሬፓብሊክ ወጣቶች በተጠሉት ፕሬዚደንቶቻቸው አንፃር በተደጋጋሚ ተቃውሞ አድርገዋል ።
|
በሴኔጋል እና በቡርኪና ፋሶም ተቃዋሚዎች አምባገነን መሪዎቻቸውን ከስልጣን አባረዋል።
|
በሌሎች አፍሪቃውያትሀገራት ግን ተቃውሞዎቹ ያን ያህል አልተሳኩም ይላሉ ፕሮፌሰር ዛካሪያ ማምፒሌ።
|
በዚህ ፈንታ ድምፃቸውን ለማሰማት ሌላ አማራጭ ያፈላልጋሉ ማለት ነው።
|
ትልቁ አደጋ ግን ተቃውሞው እንዴት እንደሚካሄድ እና ምን እንደሚያስከትል መተንበይ አለመቻሉ ነው።
|
እቅዱ በአፍሪቃ የወጣቶች ሰነድ የተቀመጡትን ዓላማዎች ከግብ የማድረስ እና የወጣቱንም አቅም በፖለቲካው እና በልማቱ ዘርፍ የማጎልበት ዓላማ ይዞ ተነስቷል።
|
ይሁን እንጂ የዚምባብዌ ተወላጇ የመብት ተሟጋች ሊንዳ ማዜሪሬ በሰነዱ ስለተቀመጡት አማላይ ቃላት መስማት አትፈልግም።
|
ኮሚሽነር ዘይኑ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ፖሊስ ኢንጅንየሩ በሞቱበት ቦታ የነበሩ ማስረጃዎች እና መረጃዎችን የሚሰጡ ሰዎችን ይዞ እየመረመረ ነው ብለዋል።
|
የአሟሟታቸውን ሁኔታ የሚያሳይ የምርመራ ውጤት ፈጥነን ለማቅረብ ርብርብ እያደረግን ነው።
|
ዉይይቱ ሲያበቃ ዛሬ ከቀትር በኋላ የነበረዉን ጋዜጣዊ መግለጫ የተከታተለዉን የብራስልስ ወኪላችን ገበያዉ ንጉሴን በስልክ አነጋግሬዋለሁ።
|
የገበያ ማዕከሉ አሁን በሚገኝበት መብራት ኃይል በተባለው ቦታ እንኳ ቃጠሎ ሲገጥመው ሁለተኛ ጊዜው ነው ፡፡
|
የገበያ ማዕከሉ አሁን በሚገኝበት መብራት ኃይል በተባለው ቦታ እንኳ ቃጠሎ ሲገጥመው ሁለተኛ ጊዜው ነው፡፡
|
መልካም እንደልሆነ አጋጣሚ ደግሞ በሁለቱም የአደጋ ክስተት ንብረታቸው ተቃጥሎ የተጎዱ ወገኖች አሉ ፡፡
|
በሌላ በኩል ነጋዴዎቹ መደበኛ ስራቸውን ለመጀመር የብድር ገንዘብ እየተመቻቸ ስለመሆኑ መስማታቸውን ገልፀዋል ፡፡
|
ምንም እንኳን እስካሁን ተግባራዊ ባይደረግም ብድር ከችግሩ አገግሞ ወደ ስራ ለመግባት አያስችልም የሚሉት ነጋዴዎች መንግሥት የተለየ ድጋፍ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል፡፡
|
ብድር ጫና ይፈጥራል የሚል ቅሬታ ስለመነሳቱ ያነሳሁላቸው ኃላፊው አብዛኞቹ ቀደም ሲል ከተቋሙ የወሰዱትን ብድር የመለሱ መሆናቸውን አረጋግጠናል ብለዋል ፡፡
|
የገበያ ማዕከሉ መልሶ ግንባታ እየተካሄደ በሚገኝበት ቦታ ተገኝቼ እንደተመለከትኩት እንዳንዶቹ ሱቆች በር በመግጠም ሥራ ለመጀመር ጥረት እያደረጉ መሆናቸውን ተመልክቻለሁ ፡፡
|
ባህል ሪታ ፓንክኸርስት የኢትዮጵያ ባለውለታ አዲስ አበባ ላይ ትዳር የመሰረቱት የኢትዮጵያ ታሪክ ተመራማሪዎች በትዳር ከ ዓመታት በላይ ዘልቀዋል።
|
ወ ሮ ሪታ ፓንክኸርስት በቤተ መፅሕፍት ባለሙያነታቸው በብሔራዊ ቤተ መፅሕፍት አገልግለዋል።
|
በኢትዮጵያዉያን ዘንድ ሕያዉ ሆነዉ ሲታወሱ ይኖራሉ ሀገራችን ሀገሯ ህዝባችን ህዝቧ ኑሯችን ኑሮዋ ሆኖ ስታገለግለን እድሜዋን ጨርሳ ከእኛው ዘንድ አረፈች።
|
ደህና ሁኚ ይላል ጋዜጠኛ የትነበርክ ታደለ በፌስቡክ ድረገፁ ያስቀመጠዉ ጽሑፍ።
|
ባለቤታቸዉ አጋፋዉ የኢትዮጵያ የታሪክ ተመራማሪ የፕሮፊሰር ሪቻርድ ፓንክኸርስት ከሁለት ዓመት በፊት ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸዉ ይታወሳል።
|
በዚህ ዝግጅታችን የሪታ ፓንክኸርስትን የሕይወት ታሪክና በኢትዮጵያ ሳሉ ያበረከቱትን አስተዋፅኦ እንቃኛለን።
|
በጎርጎረሳዉያኑ ዓ ም በሩሜንያ የተወለዱት ወ ሮ ሪታ ፓንክኸርስት በ ዓመታቸዉ ከወላጆቻቸዉ ጋር ወደ እንጊሊዝ ተሰደዱ።
|
ታዳጊዋ ሪታ በእንጊሊዝ ሃገር ካምብሪጅ ከተማ በሚገኝ የልጃገረዶች ት ቤት የአንደኛ እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸዉን ተከታትለዋል።
|
የከፍተኛ ትምህርታቸዉን በኦክስፎድ ዩንቨርስቲ ፈረንሳይኛና ሩስያንኛን በሚያካትተዉ የዘመናዊ ቋንቋች ጥናት በማስተርስ ዲግሪ ተመርቀዋል።
|
ሪታ የከፍተኛ ትምህርታቸዉን እንዳጠናቀቁ በመጀመርያ የተቀጠሩት ቻተም ሃዉስ በሚገኘዉ ፕሬስ ቤተ መፅሕፍት ዉስጥ ነዉ።
|
ከዝያም ሪታ የዝያን ግዜ የፍቅር ጓደኛቸዉ ሪቻርድን እና የሪቻርድን እናት ሲልቪያ ፓንክኸርስትን ተከትለዉ ወደ ኢትዮጵያ በጎርጎረሳዉያኑ ዓ ም ይመጣሉ።
|
የሪታ ፓንክኸርስት ልጅ አሉላ ፓንክኸርስት ስለእናቱ ማንነት እንዲነግረን ቀጠሮ ልንይዝ የደወልነት በለቅሶ ላይ ሳለ ነበር።
|
እንድያም ሆኖ ለነገ ቀጠረንና ግንቦት የእናቱ ግባዕተ መሬት ከተፈፀመ ከአንድ ቀን በኋላ በስልክ ስለናቱ አጫወተን።
|
እናቱ ሪታ በብሪታንያ የከፍተኛ ትምህርታቸዉን አጠናቀዉ በመፀሐፍ ትርጉም በቋንቋ አስተማሪነት እንዲሁም በቤተ መፅሐፍ ዉስጥ ሲሰሩ ሳለ ሪቻርድን ይተዋወቃሉ።
|
ሪታ እናቴ አባቴን እንደ አጋጣሚ ለንደን ከተማ ላይ ተዋዉቃዉ ነበር።
|
አባቴ ከእናቴጋር ወደ ኢትዮጵያ ለመሄድ መወሰኑን ነግሮ አብራ እንድትመጣ ጋበዛት እስዋም ወድያዉኑ ከሱ ጋር ወደ ኢትዮጵያ ለመሄድ ወሰነች።
|
እናት እና አባትዋ ወደ ኢትዮጵያ ለመሄድ መወሰንዋን ሲሰሙ በጣም ሰግተዉ ነበር።
|
በዚሁ ዓመት እናትና አባቴ እዚሁ አዲስ አበባ ጋብቻቸዉን ፈፀሙ።
|
ሚዜዎቻቸዉ ሜትር አርቴስት አፈወርቅ ተክሌ እና መንግስቱ ለማ ነበሩ።
|
አዲስ አበባ ላይ ትዳር የመሰረቱት የኢትዮጵያ ታሪክ ተመራማሪዎች በትዳር ከ ዓመታት በላይ ዘልቀዋል።
|
በረጅም ዓመታት የስራ ዘመናቸው ወ ሮ ሪታ የኢትዮጵያን ባሕል የኢትዮጵያውያን ሴቶች ታሪክን እንዲሁም በኢትዮጵያ የቤተ መፅሕፍት ታሪክና ዕድገትን መርምረዋል ዘክረዋል።
|
ወደ ለንደን የተሰደዱት በወቅቱ በሃገሪቱ በነበረዉ አስከፊ ሁኔታ ልጆቻችንን ለማሳደግ ከባድነ ነበር የሚል ስጋት አድሮባቸዉ ስለነበረ ነዉ።
|
እግረ መንገድዋን አባቴ ሪቻርድ በሚያዘጋጀዉ ኢትዮጵያን ኦብዘርቬሽን በተባለዉ መጽሔት ላይ በጽሑፍ ታግዘዉ ነበር።
|
በቤተ መጻሕፍት በተለይ የአጼ ቴድሮስ በብራና ላይ የተፃፉ ደብዳቤዎችን እና ጽሑፎችን በተመለከተ የተለያዩ ጽሑፎችን በማቅረብ አስተዋዉቃለች።
|
አቶ አሉላ በቀይ ሽብር ጊዜ ወላጆቼ እኛን ይዘዉ ወደ ብሪታንያ ተሰደዉ ነበር ብለኸኛል እስቴ ስለ ስደት ታሪክ ንገረን
|
ኑሮዋቸዉ ሙሉ በሙሉ እዚሁ ኢትዮጵያ አዲስ አበባ ዉስጥ ነበር።
|
ደርግ ወደ ስልጣን በመጣ ጊዜ መጀመርያ ሁኔታዉ ተቀይሮ ብሩህ ተስፋ ይመስል ነበር ።
|
አማን አብዶ የአባቴ ተማሪ ነበር በጣም ጎበዝ ተማሪ በጣም የሚያደንቀዉ ተማሪ ነበር።
|
አካባቢዉ ላይ ታንኮች ገብተዉ አማን አብዶ በተገደለ ጊዜ እና ሁኔታዉ አሳሳቢ እየሆነ ሄደ።
|
አባቴ እንግሊዝ ለንደን እንደገባ ስራ አልነበረዉም ከዝያም ለንደን በሚገኝ ዩንቨርስቲ የአፍሪቃ ጥናት ተቋም ዉስጥ ለማስተማር የአንድ ዓመት ኮንትራት አገኘ።
|
እናቴም በቤተ መፅሐፍት ጉዳይ ሞያ በለንደን በአንድ ዩንቨርስቲ ዉስጥ ስራን ጀመረች።
|
እንድያም ሆኖ ወላጆቼ ለንደን ይኑሩ እንጂ ሃሳባቸዉ ወደ ኢትዮጵያ ነበር።
|
በዝያዉ በለንደን ሲኖሩ የመጀመርያዉ የኢትዮጵያ ሥነ ጥበብ የዓለም አቀፍ ጉባኤ ለንደን ላይ እንዲጀመር አብረዉ ነበር ስራን የሰሩት።
|
ከዝያም አባቴ ወደ ኢትዮጵያ የመመለስ እድልን ሲያገኝ ለመመለስ ፈለገ።
|
ከዝያም አባቴ ተመልሶ በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ በኢትዮጵያ ጥናት ተቋም ማገልገል ጀመረ።
|
እናቴም እንዲሁ የተለያዩ የጥናት ጽሑፎችን እንዲሁም የተማሪዎች የመመረቅያ ጽሑፎችን አርትዓይ በማድረግ ሥራን መስራት እገዛን ጀመረች።
|
ለምሳሌ ለኢትዮጵያዉያን ወጣት ተማሪዎች በየዉጭ ትምህርት እድል እንዲያገኙ በአንድ ዓለም አቀፍ ተቋም ዉስጥ በመስራት ትልቅ እገዛን አድርጋለች።
|
በተለይ ግቢዋ ዉስጥ የምትተክላቸዉን የተለያዩ ተክሎች አበቦች በጣም ትወድ ነበር።
|
በዚህም ወጣት አታክልተኞችን ለማበረታታት በሚደረገዉ እንቅስቃሴ ከፍተኛ ስተዋጾን አበርክታለች።
|
በሃገሪቱ በሚካሄድ የአትክልት ትርኢት ዉድድር ላይ በዳኝነት ወንበር ላይ ትቀመጥ ነበር።
|
ወ ሮ ሪታ ፓንክኸርስት ባለፉት ስድስት አምስት ዓመታት ከባለቤታቸዉ ጋር በመሆን የኢትዮጵያ ታሪካቸዉን መፃፍ ጀምረዉ ነበር።
|
ኢትዮጵያን ወዳጅዋ ሲቭሊያ ፓንክኸርስት ለኢትዮጵያ ሰርተዉ እዉቀት ፍቅርን አስተላልፈዉ አልፈዋል።
|
የፓንክኸርስት ቤተሰቦች ለኢትዮጵያዉያ ያበረከቱት ከፍተኛ አስተዋፅዖ ትዉልድ ሲማርበት እንዲሁም በስራቸዉ በኢትዮጵያዉያን ዘንድ ሕያዉ ሆነዉ ሲታወሱ ይኖራሉ።
|
አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ከገዢው ፓርቲ የተለመደ ይትባህል ወጣ ባለ መልኩ ያቀረቡት ንግግር ብዙዎች ተስፋ እንዲሰንቁ አድርጓቸዋል፡፡
|
ከሀገር ውስጥም ሆነ ከውጭ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ በቶሎ ማሻሻያዎችን እንዲተገብሩ የሚጠይቁ ደጋግመው የሚያነሱት አንድ ጉዳይ አለ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ፡፡
|
ባለፈው የካቲት ወር የታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ድንጋጌ ለስድስት ወር እንደሚቆይ ቢቀመጥም ጠያቂዎቹ ግን አሁኑኑ ይነሳ ባይ ናቸው፡፡
|
ይህንን አቋማቸው በይፋ ካሳወቁት መካከል የኢትዮጵያ መንግስት ሁነኛ አጋር የሚባሉት አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት ይገኙበታል፡፡
|
የአሜሪካንን ፈለግ የተከተለ የሚመስለው የአውሮፓ ህብረትም አዋጁ በቶሎ እንዲነሳ ፍላጎቱን ገልጿል፡፡
|
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በአዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ለ ቀናት ያህል ታስሮ ባለፈው ሳምንት ተለቅቋል፡፡
|
በእስር በቆየበት የፖሊስ መምሪያ ውስጥ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ጥሳችኋል በሚል ወደ ገደማ ተጠርጣሪዎች ታስረው መመልከቱን ይናገራል፡፡
|
አብዛኞቹ የተከሰሱበትን ጉዳይ ግን እንኳ በቅጡ እንደማያውቁ እና ሲያዙም ድብደባ እንደተፈጸመባቸው እንደነገሩት ይገልጻል፡፡
|
የፉሪ የወንጀል መከላከል ኃላፊ ኮማንደር አየለ ደበላ እና የፉሪ የትራፊክ ፖሊስ ኃላፊ አለ፡፡
|
አብዛኞቹ የመጡት ከአዲስ አበባ እና ከአዲስ አበባ ዙሪያ ነው፡፡
|
ለምሳሌ አንድ አማረ የሚባል መካኒሳ ጋር የተያዘ ፌስ ቡኩን እያየ የኮሎኔል ደመቀን ፎቶ አጋርተሃል ተብሎ ነው የመጣው፡፡
|
በሙሉ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተይዘው እኛ የነበርንበት ፖሊስ ጣቢያ ያሉ ከቤታቸው ከስራ ቦታቸው እና ከመንገድ ላይ የተያዙ ናቸው፡፡
|
እነርሱ አሁን ከእኛ የተለየ የሚያደርጋቸው ከፍተኛ ድብደባ ተፈጽሞባቸዋል በተያዙበት የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ቀን ላይ፡፡
|
አሁን ሲያዩን አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከመውጣቱ በፊት በአመጽ ወቅት ላይ ተሳትፎ ነበራችሁ ነው፡፡
|
ከአዲስ አበባ በስተሰሜን ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ባህር ዳርም ተርጣሪዎች የተያዙበት ሁኔታ ተመሳሳይ እንደሆነ የዓይን እማኞች ይናገራሉ፡፡
|
የባህር ዳር ዩኒቨርስቲው መምህር እና ጓደኞቻቸው በቆዩበት ፖሊስ ጣቢያ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የታሰሩ ቁጥራቸው ወደ የሚጠጉ ሰዎች እንዳጋጠሟቸው ይናገራሉ፡፡
|
ባህር ዳር ከነማ ከደሴ ከነማ ጋር በነበረው ጨዋታ ዕለት ረብሻ ፈጥራችኋል ተብለው ተይዘው የነበሩ ወደ ወይም ልጆች ነበሩ፡፡
|
እንዲዚህ አይነት በትንንሽ ጉዳዩች ጽሁፍ በኪሳችሁ ይዛችሁ ስቴድየም ተገኝታችኋል ተብሎ የታሰሩ ልጆች ነበሩ፡፡
|
እንደዚህ አይነት ልጆች ዘጠነኛ ፖሊስ ጣቢያ ብዙ እስረኛ ነው የነበረው፡፡
|
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ማስፈጸሚያ መመሪያ በመላው ሀገሪቱ የሚተገብሩ ብሎ ክልከላዎችን የዘረዘረ ሲሆን ለተወሰኑ ቦታዎች ደግሞ አራት ክልከላዎችን አስቀምጧል፡፡
|
አዋጁን እና መመሪያውን የፈተሹ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማት ክልከላዎቹ አሻሚ ትርጉም ያላቸው እና ግልጽነት የሚጎድላቸው ናቸው ሲሉ ይተቻሉ፡፡
|
መመሪያ ተብሎ የወጣውን የኢትዮጵያ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማስፈጸሚያ ደንብ ስታየው ህግ በሚያረቅቁ ሰዎች ተጽፏል ብሎ ለመናገር በጣም ነው የሚያሳፍረው፡፡
|
ስለ አመክኖያዊ ትስስራቸው መሬት ላይ ሲተገበሩ ስለሚያመጡት ውጤት ምን ያህል ተጨባጭ ናቸው
|
ምን ያህል ከሰው እና ከማህበረሰብ የቀን ተቀን መስተጋብር ጋር አብረው ይሄዳሉ ስለሚለው ጉዳይ ብዙም ትኩረት የተሰጠ አይመስለኝም፡፡
|
ለህግ ደንቦች አረቃቀቅ ምንም ክብር በሌለው ሁኔታ የተረቀቀ አይነት ነው፡፡
|
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ላይ ያሉ ድንጋጌዎች በስፋት የተቀመጡ እና አሻሚዎች የሆኑ ናቸው፡፡
|
ምርመራ ለምን ያህል ጊዜ ያህል ይካሄዳል የሚሉት እንደዚሁ የሉም፡፡
|
ታሳሪዎቹ አላግባብ መታሰራቸውን የት አቤት ማለት እንደሚችሉ ለማወቅ ተቸግረዋል።
|
በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ወቅት የሚወሰዱ እንደዚህ አይነት እርምጃዎችን የመከታተል እና የመቆጣጠር ተግባር ያለው መርማሪ ቦርድ ግን ስራየን እያከናወነንኩ ነው ይላል።
|
መርማሪ ቦርዱ በአዋጁ የሚወሰዱ እርምጃዎች ኢ ሰብዓዊ መሆናቸውን ካመነ እርምጃውን እንዲያስተካክል ለኮማንድ ፖስቱ ሀሳብ እንደሚሰጥ ተደንግጓል፡፡
|
ቦርዱ ከተሰጠው ስልጣን እና ተግባር አንዱ በአዋጁ ምክንያት የታሰሩ ግለሰቦችን እና የታሰሩበትን ምክንያት በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ይፋ ማድረግ ነው፡፡
|
አራማጆች አክቲቪስቶች ግን በየአካባቢው የታሰሩ ሰዎች በቦርዱ ከተጠቀሰው በጣሙኑ እንደሚልቅ ይሟገታሉ።
|
የቦርዱ ሰብሳቢ በባለፈው ሳምንት መግለጫቸው ከህብረተሰቡ ከሚደርሷቸው ጥቆማዎች ብዙዎቹ ሰዎች እየታሰሩ ያሉት በቂም በቀል ነው የሚል እንደሆነ አስረድተዋል፡፡
|
ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ በስልጣን ላይ በቆየባቸው ዓመታት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሲያውጅ የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜው ነው፡፡
|
ባለፈው ዓመት ታውጆ የነበረው ተመሳሳይ ድንጋጌ ለ ወር ከቆየ በኋላ እንዲነሳ ተደርጓል፡፡
|
በሚኒስትሮች ምክር ቤት አማካኝነት በየካቲት የታወጀው የአሁኑ ድንጋጌ ሕገ መንግስቱን እና ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን ከአደጋ ለመከላከል በሚል እንደነበር ይታወሳል፡፡
|
የአምቦው ዩኒቨርስቲ መምህር ኢትዮጵያ አሁን ባለችበት ነባራዊ ሁኔታ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አስፈላጊ ነው ብዬ አላምንም ባይ ናቸው።
|
መቀመጫቸውን ዋሽንግተን ዲሲ ያደረጉት የሰብዓዊ መብቶች ህግ ባለሙያው አቶ ዩሴፍ ተመሳሳይ አስተያየት አላቸው፡፡
|
በዓረብኛ ፊደል የተገኙ የኢትዮጵያ የፅሁፍ ቅርሶች መግቢያ ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን።
|
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.